Page 1 of 2

በሶማሊያ መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ላይ የጂሃድ ጥሪ አወጁ?

Posted: Mon Jan 08, 2024 4:24 am
by dan

በሶማሊያ መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ላይ የጅሃድ ጦርነት እንዲታወጅ ጥሪ ቀረበ። የሶማሊያ ወጣቶች መንግስታቸው ከአልሸባብ ጋር ተባብሮ እንዲሰራ ጠይቀዋል። የሚሉ ዜናዎች እየተሰሙ ነው። እውነት ነወይ? ከሆነ ምን ማለት ነው? የጅሃድ ጥሪያቸውን ማነው የሚመልሰው?


Re: በሶማሊያ መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ላይ የጂሃድ ጥሪ አወጁ?

Posted: Mon Jan 08, 2024 9:30 pm
by Baykedagn

የጅሃድ ጥሪ በኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ከሽፏል። የማይሆን ምኞት ነው። ሁለቱም አገራት ችግራቸውን በንግግር እንደሚፈቱ እገምታለሁ። ለጦርነት የሚሆን ጉልበት የላቸውም አጉል መወራጨት ካልሆነ በስተቀር።


Re: በሶማሊያ መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ላይ የጂሃድ ጥሪ አወጁ?

Posted: Tue Jan 09, 2024 10:40 pm
by gebetaforum

ውድ ዳን መችና በየትኛው የመገናኛ ብዙሃን ይህ ጥሪ እንደተላለፈ መረጃው ካሎት ሊያካፍሉን ይችላሉ? የዜናዎ ምንጭ ማን ነው?

dan wrote: Mon Jan 08, 2024 4:24 am

በሶማሊያ መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ላይ የጅሃድ ጦርነት እንዲታወጅ ጥሪ ቀረበ። የሶማሊያ ወጣቶች መንግስታቸው ከአልሸባብ ጋር ተባብሮ እንዲሰራ ጠይቀዋል። የሚሉ ዜናዎች እየተሰሙ ነው። እውነት ነወይ? ከሆነ ምን ማለት ነው? የጅሃድ ጥሪያቸውን ማነው የሚመልሰው?


Re: በሶማሊያ መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ላይ የጂሃድ ጥሪ አወጁ?

Posted: Wed Jan 10, 2024 3:56 am
by dan

በማሕበራዊ ሚድያ ሲዘዋወር ነው የሰማሁት። ቋንቋውን ስለማልሰማ ትክክለኛው ምንጭ ማቅረብ አልችልም። የኔ ጥያቄ በመንግስታዊ የሚድያ አውታሮች ጥሪው ቢተላለፍስ በአገራችን የሚያስከትለው ነገር ይኖራል ዎይ? ከሀይማኖት መሪዎች ምን ይጠበቃል? ለማለት ነው።


Re: በሶማሊያ መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ላይ የጂሃድ ጥሪ አወጁ?

Posted: Wed Jan 10, 2024 9:35 pm
by Jemal

ሠላም የዚህ ፎረም ተሳታፊዎች

አቶ ዳን ምነው ባልተጣራ ዜና እስልምና ላይ ጣት ይቀስራሉ። ጨዋዉን የሙስሊሙ ማህበረሰብ አያውቁትም እንዴ። ከማንም በፊት ቀድሞ ሰላማዊ ትግል በአገራችን ኢትዮጵያ ያስተዋወቀው ሙስሊሙ ማህበረሰብ መሆኑ አያስታውሱም እንዴ? ይህን ከማንም በፊት ቀድሞ የነቃ ማህበረሰብ እንዴት ቢንቁት ነው ለማንም ኩታራ ጥሪ ምላሽ ይሰጣል ብለው የገመቱት? የኢትዮጵያ ሙስሊም ከእስልምና እምነቱ እኩል አገሩን ያከብራል። ምንም እንኳን ሁሌም እንደባይተዋር እየታየ የኖረ ማህበረሰብ ቢሆንም ለኢትዮጵያ ህይወቱን ሲሰጥ የኖረ ህዝብ ነው። ለዚህ ህዝብ ክብር እንጂ እንዲህ ያለ የወረደ ነገር አይገባውም። መልካም ምሽት


Re: በሶማሊያ መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ላይ የጂሃድ ጥሪ አወጁ?

Posted: Thu Jan 11, 2024 6:27 am
by dan

ዌልካም አቶ ጀማል! (ዞረው ካልገቡ በስተቀር :lol: ) እንደ እንግዳኖቶ በዌልካም ብቻ ልቀበሎ። እንጂ ተላልፈናል።

Jemal wrote: Wed Jan 10, 2024 9:35 pm

ሠላም የዚህ ፎረም ተሳታፊዎች

አቶ ዳን ምነው ባልተጣራ ዜና እስልምና ላይ ጣት ይቀስራሉ። ጨዋዉን የሙስሊሙ ማህበረሰብ አያውቁትም እንዴ። ከማንም በፊት ቀድሞ ሰላማዊ ትግል በአገራችን ኢትዮጵያ ያስተዋወቀው ሙስሊሙ ማህበረሰብ መሆኑ አያስታውሱም እንዴ? ይህን ከማንም በፊት ቀድሞ የነቃ ማህበረሰብ እንዴት ቢንቁት ነው ለማንም ኩታራ ጥሪ ምላሽ ይሰጣል ብለው የገመቱት? የኢትዮጵያ ሙስሊም ከእስልምና እምነቱ እኩል አገሩን ያከብራል። ምንም እንኳን ሁሌም እንደባይተዋር እየታየ የኖረ ማህበረሰብ ቢሆንም ለኢትዮጵያ ህይወቱን ሲሰጥ የኖረ ህዝብ ነው። ለዚህ ህዝብ ክብር እንጂ እንዲህ ያለ የወረደ ነገር አይገባውም። መልካም ምሽት


Re: በሶማሊያ መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ላይ የጂሃድ ጥሪ አወጁ?

Posted: Fri Jan 12, 2024 5:07 pm
by gebetaforum

የዚህን ዜና እውነተኛነት ለማረጋገጥ ስንበረብር፣ የአልሸባብ ቃል አቀባይ ከ10 ቀናት በፊት ይህን ጥሪ ማድረጋቸውን የሚጠቁም መረጃ አገኘን። ለጊዜው በየትኛው ሚድያ ይህን ጥሪ እንዳስተላለፉ ለማወቅ አልቻልንም። ይዘቱን እዚህ ላይ ለጥፈነዋል።

የወደብ ስምምነቱ የፈጠረው ውጥረት አልሸባብን የሚያጠናክር መሆኑን የገመተው ጽሁፍ፣ ብዙም ሳይቆይ ከሳምንት ብኋላ አል ሸባብ የተመድ ሄልኮፕተር ጠልፏል። በውስጧ የነበሩ ሰዎች እስካሁን የት እንዳሉ አልታወቀም። ፖሊስ አሰሳውን እንደቀጠለ ነው።
ጽሁፉ አልሸባብ ኢትዮጵያን እንደ እስራኤል እንደሚመለከታት ይገልጻል። እስራኤል ቀስ በቀስ ፍልስጤምን እንደሰለቀጠቻት ሁሉ የኢትዮጵያም ፍላጎት ሶማሊያን መሰልቀጥ ነው ይላል። ስለሆነም ለጅሀድ ተነሱ የሚል ጥሪ ማስተላለፉ ታውቋል።

ይህ አይነት ጥሪ በአልሸባብ ሁሌም ሲባል የኖረ እንደመሆኑ መጠን ብዙም ትኩረት ላንሰጠው እንችላለን። ነገር ግን ኢትዮጵያ ውስጥ የተፈጠረውን ክፍፍልና ቀውስ እንዲህውም ሶማሊያ ላይ እየተፈጠረ ያለው ናሽናሊስቲክ እንቅስቃሴ ተዳብለው ኢትዮጵያ ላይ ጥቃት መሰንዘር አይችሉም ብሎ መገመት ያስቸግራል።