የስብሓት ማስታወሻ

በእግዚአብሔር አምናለሁ … ፓርቲው ደግሞ እግዚአብሔር የለም ይላል … ስለዚህ እኔ ለመንግሥት በመሥራት ማገልገል እንጂ በሃይማኖቴ ምክንያት የፓርቲው አባል ልሆን የተፈቀደልኝ አይደለሁም።

ዘነበ ወላ፦ “ጋሼ፣ የማርክስን ፍልስፍና አንብበው የሰው ልጆች አልተረዱትም ወይስ ተግባራዊነቱ ላይ ነው ያልሰመረላቸው?”

ስብሐት፦ “ይኸውልህ፣ እንደ ማነኛውም ወንጌል ነው የማርክስ ወንጌል። ለድሆች ደህንነት የቆመ ነው። ከኢየሱስ ወንጌል የሚለየው በአንድ ነገር ብቻ ነው። ይኸውም ገነትን እዚሁ መሬት ላይ እንዘረጋለን ይልሃል ማርክስ። ሠራተኛው መደብ ያሸንፋል ነው ትንቢቱ። አብዮታዊ ፓርቲ ለጭቁኑ አገልግሎት ነው የሚዋቀረው።”

ዘነበ ወላ፦ “ለተከተሉት ሰዎች የማርክስ ፍልስፍና በተግባር ሊተረጎም ይችላል ነው የምትለኝ?”

ስብሐት፦ “ሊተረጎም ካልቻለ የማይቻል ቢሆን እኮ ነው። እንጂ ማርክስ ሃሳቡ በጣም ልክ ነበር። ሃሳቡን እንይ። ከሁሉም እንደችሎታው ለሁሉም እንደሚያስፈልገው ነው የሚለን። ኅብረተሰብ እንደ አንድ ሰው ሆነ ማለት ነው። ሀብቱ በሙሉ የጋራ ነው። ለማንም አናዳላም። ድል ስናደርግ መደብ አይኖርም ወገን አይኖርም። እንደዛ ነው ትንቢቱ። ለእኔ ህልም ነው። ግን ሰው ያለ ህልም አይኖርም።

‘እኔ ቀርቶ እኛ ሆኗል’ በማለት ማርክሲስት ነን የሚሉ ፓርቲዎች አዲስ ገዢ መደብ ሆኑ። ምንም አልተለወጠም። እነሱም የሚፈልጉትን ያገኛሉ ህዝቡም ለጥቂቱ ነገር ይሰለፋል። ‘ይበልጥ ሲለወጥ ይበልጥ ያው ነው’ ይለናል ፈረንሳይ።

የአሜሪካ ሠራተኞች ግን ማርክሲዝምን በሥራ ላይ አዋሉት። ተደራጁ። ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው እንዲከበር በሥራ ማቆም አድማ ጠየቁ። የሥራ ሰዓታቸው በቀን 8 ሰዓት ብቻ እንዲሆን ታገሉና አሸነፉ። ዝቅተኛው የቀን ሠራተኛ ደመወዙ በቀን ቢያንስ 10 ዶላር እንዲሆን ሠራተኛው በጥፋት ካልሆነ ከሥራው ቢሰናበት ካሣ እንዲያገኝ የተደረገው በአሜሪካን ሀገር ነው። በእስፖንዳ ማርክሲዝምን በደንብ ተጠቀሙበት።”

ዘነበ ወላ፦ “የፓርቲ አባል ነበርክ?”

ስብሐት፦ “የፓርቲ አባል አልነበርኩም! ብሆን ጥሩ ነበር። እኔ ግን ‘atheist’ አይደለሁም … በእግዚአብሔር አምናለሁ … ፓርቲው ደግሞ እግዚአብሔር የለም ይላል … ስለዚህ እኔ ለመንግሥት በመሥራት ማገልገል እንጂ በሃይማኖቴ ምክንያት የፓርቲው አባል ልሆን የተፈቀደልኝ አይደለሁም አልኳቸው። ተውኝ።”

ዘነበ ወላ፦ “የማሌ ጥናት ተብሎ በየመሥሪያ ቤቱ የውይይት ክበብ ስብሰባ ይካሄድ ነበር። በውቅቱ እንድትሳተፍ ተጠይቀህ አታውቅም?”

ስብሐት፦ “ምንድነው ማሌ?”

ዘነበ ወላ፦ “የማርክሲስት ሌኒንስት ፍልስፍና ውይይት”

ስብሐት፦ “በፍጹም። እነሱም አያስገድዱኝም። እኔም አልቀላቀላቸውም። ሰውየው ካርል ማርክስ አሪፍ ፈላስፋ ነበር። ሰዎቹ ግን ሳይገባቸው ፈተፈቱት። ፍትፈታውንም ውይይት ክበብ አሉት።”

ዘነበ ወላ፦ “የቤተ ክህነት ሰዎች መጥተው አቶ ስብሐት ይምጡ እስቲ ዘር ማንዘሮት የቤተክርስቲያኒቱ አገልጋይ ነበሩ። እርሶም የዘር ማንዘሮን ክርስትያናዊ ግዴታ ለመወጣት ቤተክህነቷ ትፈልጎታለች። መጥተው ያገልግሏት ቢሉህስ?”

ስብሐት፦ “የእኔን ተፈጥሮ ልብ በል። አንድ ‘formula’ ተከትሎ ያችኑ መደጋገም ደስ አይለኝም። በክርስትና በእስልምና በፖለቲካ ፓርቲም እያልክ ብታጠናቸው አማኞቻቸውን ደንግገው የሚይዙበት ሕግጋት አላቸው። ያ ደግሞ ሼል ሆኖ እንደ ዕንቁላል ቅርፊት ሌላን የምታይበትን ዓይን ይጋርድሃል። ስለዚህ ምንም ዓይነት የፖለቲካም ሆነ የሃይማኖት ድርጅት ተከታይ መሆን አልፈልግም።

አባቶችን፣ ቤተክህነትን ማገልገል ከአማኝ የሚጠበቅ ነው … እናንተም ከልባችሁ ቤተክህነቷን እያገለገላችኋት ነው … እኔም እንደናንተ እንዳላገለግል ‘atheist’ ነኝ እላቸዋለሁ።”

የእንስሳት ዕድር

Orwel

ተጠየቅ

ከማእድን ሚንስቴር ድረገጽ የተገኘ መረጃ እንደሚያሳየው ኢትዮጵያ ከወርቅ ቀጥሎ እምቅ የplatinum, copper, potash, natural gas እና hydropower ሀብት አላት፣ tantalum የሚባል ማዕድን ለዓለም ገበያ ኤክስፖርት ከሚያደርጉ ግንባር ቀደም አገራት መካከል አንዷ ናት፣ ከነዚህ ማዕድናት በተጨማሪ ሰፊ የniobium, platinum, tantalite, cement, salt and gypsum, clay and shale, and soda ash ክምችት እንዳላት ይገለጻል። ነገር ግን ከዚህ ዘርፍ የሚገኘው ገቢ ከአገሪቱ አመታዊ ገቢ አንድ መቶኛ (1% በታች) እንደሆነ ነው የሚነገረው። ትኩረት ተነፍጎት ነው? ሌብነት ነው? ወይስ በቂ የተማረ የሰው ሃይል ስሌለ ነው?

ተፈጥሮ ለኛ አድልታ የለገሰችንን ሀብት እንዴት በአግባቡ መጠቀም ይሳነናል? የወርቅ ክምችቱማ ፈረንጆቹን አፋቸውን በመዳፋቸው አስይዟቸዋል። አገሪቱ ያልተነካ የወርቅ ክምችት ላይ ነው የተቀመጠችው ሲሉ ይደመጣሉ።። እነ Apple በየቦታው ለጉድ የሚቀራመቱት cobaltም በአገራችን እንደሚገኝ ይገለጻል። ነዳጅ መገኘቱንም ሰምንተን ነበር።። ሠፊ፣ ለምና ውሃ ግቡ የሆነ የእርሻ መሬትም ታድለናል። ከምንም በላይ ደግሞ በአፍሪካ ከትላልቅ አገራት ተርታ የሚመድበት የሰው ሀብት፣ የህዝብ ብዛት አለን። በብዙዎች ለገበያ ይፈለጋል። ደጃችንን የሚጠኑ የውጭ ባለሀብቶች ብዙ ናቸው። (በዛው ልክ ሲያኮርፉ ባልበላው ለምን አልበትነው የሚሉም ብዙዎች ናቸው።)

ጂኦፖለቲካሊ ተፈጥሮ ቁልፍ ቦታ ላይ አስቀምጣናለች። ከአሜሪካና እስራኤል ጀምሮ እስከ ቻይናና ራሽያ እንዲህውም ዓረብ አገራት ድረስ የሚያፋጭ ቁልፍ ቦታ ላይ ተቀምጠናል። የአየር ጸባዩ፣ ብዝሀ ህይወቱ፣ ምኑ ተፈጥሮ ለኛ ማዳላቷን የሚመሰክሩ ልዩ ሀብታችን ናቸው። ልክ እንደዚህ ሁሉ የባህል ብዝሀነቱ ጥሬ ሀብት ነበረ። በቋንቋ፣ በብሔር፣ በእምነት፣ በቆዳ ቀለም፣ ዳይቨርሲፋይድ የሆኑ፣ ነገር ግን ለምዕተ ዓመታት አብረው መኖር የቻሉ፣ ከዛም አልፈው ከአንድም ሁለት ሶስቴ ከውጭ ወራሪ ራሳቸውንና አገራቸውን ተባብረው ማስጠበቅ የቻሉ፣ የዓለምን ታሪክ እስከወዲያኛው የቀየሩ፣ የራሳቸው ፊደላት ቀርጸው ታሪካቸውን በጽሁፍ ማኖር የቻሉ ዜጎች ኖረው ያለፉባት፣ በአንድ ወቅት ገናና ኢምፓየር የነበረች አገር ባለቤት ነበርን።

ይህን ሁሉ የተፈጥሮ ፀጋ፣ የቅርስና የታሪክ ሀብት ታቅፈን ከአፍንጫችን ጫፍ በላይ አሻግረን ማየት ስለተሳነን፣ የራሳችንን ህይወት ከመቀየር አልፎ እንደ አያቶቻችን ዓለምን መለወጥ የምንችልበት እድል እያለን፣ ራእይ አልባ ሆነን በመንደር ታጥረን፣ እርስ በእርስ እየተፋጀን እውቀትና ቴክኖሎጂ ባልነበረበት ግዜ ከኖሩት አያት ቅድመ አያቶቻችን የከፋ የድንቁርና የፅልመትና የውርደት ኑሮ እንኖራለን። መቼ ነው ክፋት የሚበቃን? መቼ ነው የምንነቃው??

ስሁል ሚካኤል – የዘመነ መሳፍንት የአጥቢያ ኮከብ

በትግራይ ክፍለ ሀገር፣ ዘንጉዊ በሚባል አገር አንድ ሽማግሌ መኳንንት ከሴት ልጃቸው ጋር ይኖሩ ነበር፣ ይላል አፈ ታሪካችን፡፡

አንድ ዕለት እቺ ልጃቸው የወደደችውን ወንድ በጭድ ስር ደብቃ ወደ ቤትዋ አስገባችው (እዚያ ጭልጥ ያለ ባላገር ውስጥ አልቤርጎ የለማ!) በዚህ ዘዴ እያስገባች ስታሳድረው አረገዘችለት፡፡ በዚያን ዘመን የሴቶቹ ልብስ በጣም ሰፊ እና ረጅም ሆኖ፣ ሴቲቱ ነብሰጡር ትሁን ወይስ ድንግል አያስታውቅም፡፡ አባትዋ ሳያውቁባት ቀንዋ ደረሰና አክስቷ ቤት ሄዳ ወንድ ልጅ ተገላገለች፡፡

እዚያው አክስትዋ ቤት እያደገ ስድስት አመት ሲሆነው ከልጆች ጋር ሲጫወት አያቱ አዩት፡፡ ፈጣን ነው ነቄ ጉልቤ! ሲያዩት የሚያስደስት፡፡ “ዋ! ምነው ፈጣሪ በፈቀደና ይሄ ጎበዝ ልጅ የልጄ ልጅ በሆነ!” ሲሉ ምኞታቸውን ተናገሩ፡፡ አብረዋቸው የነበሩ ሰዎች ይህን ለልጃቸው አክስት ተናገሩ፡፡

አክስት ልጁን ወስደው ለአያትየው አስረከቡ፣ የምስራች እልል እያለ፡፡ አያት ቆፍጣና ጀግና ይሆንላቸው ዘንድ በጥንቃቄ አሳደጉት፡፡ ሲጎረምስ የጎበዝ አለቃ ሆነ፡፡ ሲጎለምስ የሰራዊት አለቃ ሆነ፡፡ የፉከራ ስሙ “ስሁል!” (የተሳለ ወይም ስለታም) ሆነ፡፡

ጎንደር ዋና ከተማ ውስጥ በልዑላን መካከል እኔ እነግስ እኔ እነግስ ፍጥጫ ሆነ፡፡ የእርስ በርስ ጦርነት እንዳይነሳ የሰጉ ተቆርቋሪዎች ለራስ ስሁል ሚካኤል ላኩባቸው፡፡ ሰውየው ትልቅ ሰራዊት በትግሬ መጮህያ በኩል አስገቡና ወድያው ጎንደርን ቁጥጥራቸው ስር አዋሉ፡፡

አዋቂዎችን ለስብሰባ ጠሩ፡፡ ንጉሱን ብገድለውስ? ሲለ ጠየቁ፡፡

“የንጉስ ደም ያፈሰሰ እንኳን እሱ ዘሮቹ ለሰባት ትውልድ አይነግሱም” አለዋቸው፡፡

አንድ ከይሲ ደብተራ ግን መጣና ለብቻቸው “ደም ማፍሰስ አያስፈልግም’ኮ “በሻሽ አንቆ ማሰናበት ይቻላል” አላቸው፡፡

አፄውን በሻሽ አንቀው ገደሉትና አፄ ሆነው ለመቀባት ወደ ማርያም ፅዮን ገሰገሱ፡፡

ካህናቱ “አትነግስም ደም አፍስሰሀል” አለዋቸው፡፡

“እኔ ደም አላፈሰስኩም፡፡ በሻሽ ነው ያነቅኩዋቸው፡፡”

በሻሽ ሆነ በሰይፍ መግደል ያው መግደል ነው ተባለ፡፡ ኩም ብለው ወደ ጎተራቸው ተመለሱ፡፡

አሰቡበትና “መንገስ ባልችል ማንገስ እችል የለ?” ብለው ወስነው፣ አንድን ደስ ያላቸውን ልዑል አነገሱ፡፡ ሁለት ሶስት አመት ከነገሰ በኋላ “የሚገዙት ግን ስሁልነታቸው ናቸው የታወቀ ነው” ወይ ስላስቀየማቸው ወይ ስለሰለቻቸው አወረደትና ሌላ ልዑል አነገሱ፡፡ አንዱን ልዑል’ማ በድጋሚ አነገሱት! ስሁል ሚካኤል እንዲህ አገር አንቀጥቅጠው እየገዙ እያለ፣ የጎጃሙ አገረ ገዥ “አሻፈረኝ! ከዛሬ ጀምሮ አንድ ግብር አልከፍልም፡፡ አገሬን እኔው ራሴ ነኝ የምገዛው” ሲል ላከባቸው፡፡

“ክተት ሰራዊት! ምታ ነጋሪት!” ብለው ወደ ጎጃም መረሹ፡፡ ሰውየው ለራሳቸው ድል ሆነው የማያውቁ አደገኛ ጄኔራል ናቸው፤ ብዙም ሳይዋጉ አመፀኛውን ድል መቱትና ተማረከ፡፡

ስሁል ሚካኤል አይቀጡት ቅጣት ሲቀጡት፣ በቁሙ ህያው እያለ ቆዳውን አስገፈፉት፡፡ ቆዳው ሰው እስኪመስል ጭድ ጠቀጠቁበት፡፡

ፈጣን መልዕክተኞች መርጠው “ንጉሰ ነገስቱ ስጋት እንዳያድርባቸው፣ በተቻለ ፈጥናችሁ ይህን ግዳይ አድርሱላቸው፡፡ ሰራዊታችን ቀስ ብሎ ይደርስባችኋል”

ከእንግዲህ ማን ያበደ ነው ስሁል ሚካኤልን የሚቃወም? እሳቸው አላወቁትም እንጂ በአንድ ሰው ደም የመጀመርያውን ቀይ ሽብር አካሄዱ (ህዝብ ሲበዛ ጊዜ ጓድ ሊቀ መንበር መንግስቱ ኃይለማርያም “ቀይ ሽብር ይፋፋም!” ብለው አውጀው ብዙ ሰው አለቀ – በሳቸው ግምት ሶስት ሺ ሰው ሞተ)

ስሁል ሚካኤለ አንዲት ባርያ ነበረቻቸው፡፡ የሷ ልጅና የሳቸው ልጅ አብሮ አደግ ናቸውና በጣም ይዋደዳሉ፡፡ አንድ አጉል ቀን ጓደኛሞቹ ይጣላሉ፡፡ ያባቱ ልጅ ነውና የስሁል ሚካኤል ልጅ ቀድሞ ጦር ወርውሮ ገደለው፡፡

የሟች እናት ከሰሰች፡፡ ግን ማን ደፍሮ በስሁል ሚካኤል ልጅ ላይ ይፈርዳል? ግድያው ትክክል ነው እያለ ሲፈርድ፣ ከዝቅተኛው እስከ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ክሷን ቀጠለች፡፡

ከፍተኛው ፍርድ ቤትም ፍርድ ገምድል ሲሆንባት ጊዜ ስሁል ሚካኤል ላይ ከሰሰች፡፡

ስሁል ሚካኤል ልጃቸውን አስጠሩት፡፡ መግደሉን አመነ፡፡

“ህጉ ምን ይላል? የገደለ ይሙት አይደለም?”

“ይላል”

“እንግድያው ሞት ፈርጄብሀለሁ” አሉትና በስቅላት ተገደለ፡፡ …

… ስሁል ሚካኤል አገር ሰጥለጥ አድርገው ሲገዙ በጣም ሸመገሉ፣ ወደ መጃጀት ደረሱ፡፡ አንድ ቀን ከታማኞቻቸው ጋር ተቀምጠው ሲመክሩ እንቅልፍ አሸለባቸው፡፡

ብንን ብለው ነቁና “እናንተ፣ ዛሬም እኛ ነን ስልጣን ላይ ያለነው?” ሲለ ጠየቁ፡፡

“አዎን ጌታዬ” አለዋቸው

“አቤት ጠላቶቻችን ምንኛ ይከፋቸው!” አሉ በሀዘኔታ፡፡

ያነበብነው በልባችን ያሳድርልን አሜን!

©ስብሓት ገ/እግዚአብሔር

Embracing Digital Minimalism, A Book Review

In today’s technology-driven world, our lives have become increasingly intertwined with a myriad of digital devices and platforms. Social media, smartphones, and an endless array of applications compete for our attention, leading to a constant barrage of notifications and a never-ending cycle of information consumption. Cal Newport’s book, “Digital Minimalism: Choosing a Focused Life in a Noisy World,” offers a refreshing alternative to this chaotic digital existence.

As an Associate Professor of Computer Science at Georgetown University and the author of several books on productivity and work habits, Newport brings his expertise to the forefront in “Digital Minimalism.” Throughout the book, he lays out a compelling argument for a more intentional and minimalist approach to technology use, offering practical tips and strategies for regaining control of our time and attention.

The core concept of digital minimalism revolves around the idea of intentionally selecting and using technology to maximize its benefits while minimizing its negative impacts on our lives. Newport emphasizes the importance of being intentional with our tech usage, encouraging readers to consciously decide which technologies serve their values and goals, rather than mindlessly consuming everything that comes their way.

One of the book’s most resonating points is the exploration of the attention economy, which posits that our attention is the most valuable resource for technology companies. Newport elucidates how these companies design their products to be as addictive and attention-grabbing as possible. By understanding the underlying mechanisms of this economy, readers can begin to see the importance of reclaiming their attention and being more deliberate with their digital choices.

“Digital Minimalism” is divided into two parts. The first part focuses on understanding the problem of digital addiction and the need for a new philosophy to combat it. Newport introduces the concept of digital minimalism and provides a historical context for the minimalist movement, drawing parallels to Henry David Thoreau’s “Walden” and other examples of minimalism in art and design.

The second part of the book is dedicated to practical solutions for adopting digital minimalism. Newport suggests a 30-day digital declutter, during which readers can temporarily disconnect from optional technologies to reflect on their values and goals. After the declutter, readers are advised to reintroduce only the technologies that align with their values and serve a specific purpose in their lives.

Newport also offers tips for cultivating high-quality leisure activities, which he believes are crucial for a fulfilling life outside of the digital realm. He encourages readers to engage in activities that require skill and concentration, such as reading, writing, or woodworking, instead of resorting to passive digital consumption. The book also addresses the importance of solitude and provides strategies for fostering meaningful social connections in the age of social media.

“Digital Minimalism” is not a call to abandon technology altogether; rather, it advocates for a more thoughtful and intentional approach to its use. Newport acknowledges the numerous benefits of technology but urges readers to adopt a more discerning attitude, striving for a balance between the digital and physical worlds.

One of the strengths of this book is its accessibility. Newport’s writing style is engaging and easy to understand, making complex ideas approachable for a wide range of readers. The book is also well-researched, incorporating a variety of studies, anecdotes, and interviews that lend credibility to the author’s arguments.

However, some readers might find Newport’s proposed solutions to be overly prescriptive or restrictive. The 30-day digital declutter, for example, may not be feasible for everyone, especially those whose work or personal lives are heavily reliant on digital communication. Additionally, while the book offers practical tips for adopting digital minimalism, it does not dive deeply into the psychological aspects of digital addiction or provide tools for managing cravings and withdrawal.

In conclusion, Cal Newport’s “Digital Minimalism” is a thought-provoking and timely exploration of our relationship with technology. It provides a compelling argument for a more intentional and minimalist approach to technology use, offering practical solutions for those seeking to regain control of their time and attention. While some readers may find the proposed solutions overly prescriptive, the book’s core message of being deliberate with our digital choices is universally applicable. Moreover, by offering a new philosophy for navigating the digital world, Newport challenges readers to rethink their habits and rediscover the importance of solitude, meaningful social connections, and high-quality leisure activities. If you’re looking for a guide to help you find balance in today’s noisy world, “Digital Minimalism” is an invaluable resource.

የኤርትራ ጉዳይ

1-ERITREA-GUDAY